Tuesday, December 18, 2018


{`ከአሜን ባሻገር`}
======
"በዘመናችን #ብሔርተኝነት ማለት ሳይደክሙ የሌሎችን የድካም ውጤት መቀማት መሆኑን አውቃለሁ። አንድ ሰው በግሉ ስኬት መቀዳጀት ሲያቅተው በጥረታቸው ብልጫ ያስመዘገቡ ግለሰቦችን ስኬት ወደ ብሄር ስኬት ለውጦ ባዶነቱን ለመሙላት ይሞክራል። ሌላው÷እልም ያለ ፈሪ ሆኖ ሳለ "የበላይ ዘር" እያለ ይፎክራል። ብብቱ ውስጥ ገብተው ካልደገፉት በቀር አልጋ ላይ መውጣት የማይችለው ሰውዬ÷ አበበ ቢቂላ በተነሳ ቁጥር "አበበ ኬኛ" እያለ ይኩራራል። በላይና አበበ ያስመዘገቡት ድል በላብና በደም የተገኘ የግለሰብ ጥረት ውጤት ነው። ድል በዘር አይተላለፍም። የአባቶች ታላቅነት በዘር ወደ ልጆች የሚተላለፍ ቢሆን ኖሮ ግሪኮች በዛሬይቱ የአውሮፓ እግር ስር እንደጉድፍ ወድቀው ባልተገኙ ነበር። ብሔርተኝነት የግለሰብ ጥረትን ሰርቆ የራስን ድክመት ለመሙላት የሚደረግ መሰሪ እንቅስቃሴ ነው።"
.
©በዕውቀቱ ስዩም
{ከአሜን ባሻገር}

No comments:

Post a Comment