Tuesday, January 15, 2019


[ በዓሉ ግርማ]
______
ከጎራው ዘልቄ እስቲ ልነጋገር
ካለ ሰው ቢወዱት ምን ያደርጋል ሀገር?
የኔ ውብ ከተማ -
ሕንፃ መች ሆነና የድንጋይ ክምር፤
የኔ ውብ ከተማ-
መንገድ መች ሆነና የድንጋይ አጥር፤
የኔ ውብ ከተማ የኔ ውብ አገር
የሰው ልጅ ልብ ነው
የሌለው ድንበር።
ህንፃው ምን ቢረዝም፣ምን ቢፀዳ ቤቱ
መንገዱ ቢሰፋ ቢንጣለል አስፋልቱ
ሰው ሰው ካልሸተተ ምንድን ነው ውበቱ?
በዓሉ ግርማ(ኦሮማይ)

Thursday, January 10, 2019

 ቴዲ አፍሮ ስለ አፍሪካ!
┈┈┈┈•••┈┈┈┈┈
.
#ኮርኩማ_አፍሪካ:
.
እንባም አይወጣ ከአፍሪካ ዓይኖች ስር
ሲያቅ ልጇን ባትጥለው ኮርክማ ባህር
ይዞ የመጣን አዲስ ሃሳብ፤
አለቀ ሰዋ ቤቷን ለቆ ሄዶ ሄዶ ሄዶ
ይዞ የመጣን አዲስ ሃሳብ፤
አለቀ የሳር ቤቷ ነዶ ግዶ ግዶ።
.
በስጋት ኮፈን ተይዞ እስራት
አዋቂው ሸሽቶ ራብ ነግሶ እርዛት
በምድሯ ሊቆይ ማንስ ይደፍራል
ታንኳ ላይ ወጥቶ ወንዝ ይሻገራል።
.
ውሃ ቢገባ በአፍሪካ መርከብ
አቤት ቢል ተጓዥ ሃሳብ ለማቅረብ
ይሰምጣል እንጂ ከባህር አብሮ
ቀዛፊው ላሳብ አይሰጥም ጆሮ
አለቀ ሰዋ ባህር ገብቶ ሄዶ ሄዶ ሄዶ
ኮርኩማ አፍሪካ....
.
ኮርኩማ ወንዝ አሻገረችው
ያንን የሰው ጫካ ባዶ አደረገችው
ተጉዞ ተጉዞ ሳይመጣ ቅርስ ይዞ
ኮርኩማ ባህር ጨመረችው
ለዛ ሃሩር እሳት ቆርጣ ማገደችው
ኮርኩማ አፍሪካ......
ስቃይ አይ ስቃይ
ከእንግዲ ይብቃ በምድርሽ ላይ
ሄዶ ለባዳ መሆን ሲሳይ።
===============
#ኦ_አፍሪካ!

ኦና አድርጌው ታሪኬን
የማንነት የእምነቴን ማህተብ
ለካ አፍሪካውነቴን ስቼዋለው፤
ውዬ አድሬ ስጀምር ማሰብ
ብርድ አይሞቅም፣ በጋ አይበርድም
ማንነትም ያው ነው፣ አይለወጥም
……ዜግነቴን ሳሰላስለው
.
ወና አድርጌው ሂወቴን
ዜግነቴን ሳፈላልገው
የማንነት የምነት ማተቤን
ጥበብ ርቄ ስቀዳ
ዜግነቴን ሳሰላስለው
እንዴት ልሁን ለወንዜ ባዳ
ዜግነቴን ሳፈላልገው
ጠምቶኝ ጠጣሁ ካ'ባይ ዙሪያ
ከሠው መጀመሪያ...!

Wednesday, January 9, 2019

ሁሉም መፅሀፍ አንባቢ የራሱ የሆነ ልምድ ይኖረዋል ብዬ እገምታለው የራሴን ልምድ ላካፍላችው ወደድሁ
አንድን መፅሀፍ አንብቤ ስጨርስ ስለመፅሀፉ የተወሰነ ማስታወሻ በደብተሬ እወስዳለው ሌላ የማደርገው ደግሞ የማነባቸውን መፅሀፍ የአገር ውስጥ ለብቻ ደራሲውን የመፅሀፉን አርዕስት በተራ ቁጥር እፅፋለው የውጪውንም እንደዛው አሁን ከመፅሀፍ ገጾች በጥቂቱ ምን አሉ የሚለውን እንደሚከተለው ጻፍኩላችሁ
ትንንሽ ጋኖች ትልልቅ ጆሮዎች አላቸው -- ሳቤላ
መምት ምንም አይደለም አለመኖር ግን ያስፈራል -- ምንዱባን
የሰው ልጅ ንፁህ ሀብቱ ህሊናው ነው -- ረቂቅ አሻራ
ከወጣት ብልጣ ብልጥ ይልቅ የሽማግሌ ሞኝ ብልህ ነው -- ሕያው ፍቅር
ጤናማ ህብረተሰብ የጤናማ ግለሰቦች ውጤት ነው -- ሰመመን
አስተውሎ ለሚያይ ይህቺ አለም ችግር ያለባት ቦታ ናት እኔም አስቸጋሪነቷን አውቄ በእናቴ ሆድ እንዳለሁ አልወለድም ብዬ ነበር ግን ተወልደናልና ከዚች አለም እስክንገላገል ድረስ በትዕግስትና በቆራጥነት ለእውነተኛው ነገር መታገል አለብን -- አልወለድም
ከውጪ የሚመጣ ምንም ነገር የለም ሁሉም ከውስጥ ነው የሚመጣው -- ሚስጥሩ
ስጥ ይሰጥሃል በሰፈርክበት መስፈሪያ ትሰፈርበታለህ -- መፅሀፍ ቅዱስ
አበቃሁ መልካም የንባብ ክረምት ለሁላችን ይሁን
@BookforEthiopia
bookforethiopia.blogspot.com